የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ከ14 የምርጫ ክልሎች የሰበሰበውን ውጤት ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚሁ መሰረት ገዢው ፓርቲ ኤኤንሲ 43 በመቶ ድምጽ በማግኘት ሲመራ ዲሞክራቲክ አሊያንስ ፓርቲ ደግሞ በ26 በመቶ ድምጽ ይከተላል።በጁሊየስ ማሌማ የሚመራው ኢኮኖሚክ ፍሪደም ፋይተርስ (ኢኤፍኤፍ) እና በደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የተመሰረተው “ኡምኮንቶ ዊሲዝዌ” ፓርቲ (ኤምኬ ፓርቲ) በተመሳሳይ 8 በመቶ ገደማ ድምጽ ማግኘታቸው ተጠቁሟል።የምርጫው የመጨረሻ ውጤት በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት ይፋ እንደሚደረግ ይጠበቃል። የቅድመ ምርጫ ትንበያዎች የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ ከ30 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በፓርላማ ያለውን አብላጫ መቀመጫ ሊያጣ እንደሚችል ግምታቸውን ያስቀመጡ ሲሆን ይህም ፓርቲው ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ጥምር መንግስት የመመስረት ግዴታ ውስጥ እንዲገባ ሊያደርገው ይችላል ተብሏል።
EBC
More Stories
የጋዛው ጦርነት የሚቆም ከሆነ ሄዝቦላ በእስራኤል ላይ ጥቃት መሰንዘሩን እንደሚያቆም አስታወቀ
የሀውቲ ታጣቂዎች በእስራኤሏ ሀይፋ ወሳኝ ኢላማ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ገለጹ
በህንድ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓት ላይ በተፈጠረ መተፋፈግ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 121 ደረሰ