የኢትዮ-ፓኪስታን የኢኮኖሚ ትብብር ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በፎረሙ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረመስቀል ጫላ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እና ከ80 በላይ የፓኪስታን ባለሃብቶች ተሳትፈዋል፡፡
በተጨማሪም የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሃና አርአያ ስላሴ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ እና ሌሎች የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
ፎረሙ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት፣ የንግድ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ያጠናክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ