የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከሳዑዲ ዓረቢያ የሰው ሃብትና ማህበራዊ ልማት ሚኒስቴር ዴዔታ አብዲልዋሃብ አልአጌል ጋር በሪያድ ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በዜጎች ሕጋዊ የሥራ ስምሪት ዙሪያ የሁለትዮሽ ምክክር ማድረጋቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ወ/ሮ ሙፈሪያት÷ በሀገራቱ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ማጠናከር በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ትኩረት እንደተሰጠው አንስተዋል፡፡
በሁለቱ ሀገራት የተጀመረው አዲስ የሥራ ስምሪት በአጭር ጊዜ ውስጥ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡንም አብራርተዋል።
ቀጣይ በሁለቱ ሀገራት መካከል ቴክኒካል ቡድን አዋቅሮ በሥራ ሂደቱ ላይ የሚገጥሙ ችግሮችና እድገቶችን እየተወያዩ ለመፍታት ሂደቱን የተሻለ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
አብዲልዋሃብ አልአጌል በበኩላቸው÷ በአዲሱ የሥራ ስምሪት ኢትዮጵያዊያን ተፈላጊነታቸው እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ አሁን የሚታዩ የአሰራር ውስንነቶች በመቅረፍ ለዘርፉ ውጤታማነት በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በሳዑዲ ካላቸዉ ተፈላጊነት አንጻር ሰራተኞችን በማሰልጠን የሥራ ስምሪቱን የተደራጀ ለማድረግ መንግስታቸው እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
FBC
More Stories
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ
የጎንጋ ህዝቦች የልማት፥ የወንድማማችነትና የአብሮነት ፎረም እየተካሄደ ነው።
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያዊያን የአንድነትና የመከባበር ኃይል የሚያሳይ ትልቅ መሰባሰቢያ መድረክ ነው ሲሉ የበዓሉ ታዳሚዎች ገለጹ።