ኢትዮጵያ የራሷ የኮሙዩኒኬሽን ሳተላይት ባለቤት እንድትሆን የአዋጭነት ጥናቱ ተጠናቆ ለሚመለከተው የመንግስት አካል ለውሳኔ መላኩን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ገለፀ፡፡የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ቤተልሔም ንጉሴ፤ ኢትዮጵያ የራሷ ኮሙዩኒኬሽን ሳተላይት ስለሌላት በአሁኑ ወቅት ከሉግዘመበርግ ኢ ኤስ ኢ ኩባንያ ኢትዮ ሳትን በመጠቀም ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡ኢትዮ ሳት ኢትዮጵያ ለሳተላይት የምታወጣውን ከፍተኛ ወጪ ከመቀነስ፣ የባህል ወረራን ከመከላከል እንዲሁም ሀገራዊ እሴትን ከማስጠበቅ አንጻር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ኃላፊዋ አንስተዋል፡፡በኢትዮጵያ ከ2014 ዓ.ም በአዲስ መልክ የተደራጀው የስፔስ ሳይንስና ጂኢስፓሻል ኢንስቲቲዩ፤ በቀጣይ ኢትዮጵያ የራሷ የኮሙዩኒኬሽን ሳተላይት ባለቤት እንድትሆን የአዋጭነት ጥናት ተጠናቆ ለፕላንና ልማት ሚኒስቴር መላኩንና ውሳኔ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
EBC
More Stories
በጤና ተቋማት የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በመከላከልና ተገቢውን የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ማድረግ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ይጠበቃል ተባለ ።
ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት ሁለተኛውን የዓርበኝነት ምዕራፍ ጀምራለች – ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ኢትዮጵያ እያስመዘገበችው ላለው ፈጣን እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው፦ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር)