የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ለማዘመን ከአዘርባጃኑ ጉብኝት ትልቅ ተሞክሮ ተገኝቷል፡- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
በኢትዮጵያ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከአዘርባጃኑ ጉብኝት ትልቅ ተሞክሮ መገኘቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትናንትናው እለት በአዘርባጃን ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም በአዘርባጃን በተለይ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል እየተሰጠ እንደሚገኝና ይህም የአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋና ምቹ እንዲሆን ማድረጉን መመልከታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በተለያዩ ዘርፎች ውጤታማ የሆነ ሪፎርም ማድረጉን ያስታወሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁን ደግሞ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ሪፎርም የማድረግ ስራዎች ተጀምረዋል ብለዋል።
EBC
More Stories
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ
የጎንጋ ህዝቦች የልማት፥ የወንድማማችነትና የአብሮነት ፎረም እየተካሄደ ነው።
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያዊያን የአንድነትና የመከባበር ኃይል የሚያሳይ ትልቅ መሰባሰቢያ መድረክ ነው ሲሉ የበዓሉ ታዳሚዎች ገለጹ።