በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የተጣበቁ መንታ ህፃናት ተወለዱበአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የፅንስና ማህፀን ስፔሻሊስት ዶክተር አረጋኸኝ ሙሉጌታ ህፃናቱ ሁለት ጭንቅላት፣ አራት እጅ፣ አራት እግር ያላቸው ሲሆን የጋራ የሆነ አንድ ልብና አንድ እትብት እንዳላቸው አስረድተው ሁለቱም ጾታቸው ወንድ መሆኑን ተናግረዋል።ለምርመራ ወደ ሆስፒታሉ ከመጡበት 8ኛ ወር ጀምሮ ክትትል ሲደረግላቸው የቆዩት እናት በቀዶ ጥገና በሠላም መገላገላቸው ተገልጿል።እንደዚህ አይነት ክስተቶች አልፎ አልፎ የሚከሰቱ መሆናቸውን ገልፀው እናቶች የእርግዝና ምርመራ በወቅቱና በአግባቡ ቢያደርጉ ችግሩ ሊፈታ የሚችልበትም አጋጣሚ አለ ብለዋል፡፡ከሆስፒታሉ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በአሁኑ ሰአትህጻናቱ እና እናታቸው በጥሩ የጤንነት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ፡፡
SRTA
More Stories
የለምጽ ምንነት እና ህክምናው
የኮሊስትሮል መድሃኒትን የሰሩት ተመራማሪ ህይወታቸው አልፈ
በኢትዮጵያ ለሕጻናት ክትባት ተደራሽነት ፕሮጀክት 45 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ተደረገ