በባሕር ዳር ከተማ በዓባይ ወንዝ ላይ የተገነባው አዲሱ የዓባይ ድልድይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምረቃው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የዓባይ ድልድይ በኢትዮጵያ ከተሰሩ የድልድይ ፕሮጀክቶች በስፋቱም በርዝመቱም ግዙፍ ፕሮጀከት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደመንግስት ሁለት ድልድይ ለመገንባት እንፈልጋለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የመጀመሪያው ልማትን የሚያሳልጥ ድልድይ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ህዝብን የሚለያይ ግድግዳ በማፍረስ የአንድነት ድልድይ መገንባት ነው ብለዋል፡፡ በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል። አዲሱ የዓባይ ድልድይ 380 ሜትር ርዝማኔ ያለው ሲሆን፤ 43 ሜትር የጎን ስፋት እንዳለውም ተጠቁሟል።
FBC
More Stories
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ
የጎንጋ ህዝቦች የልማት፥ የወንድማማችነትና የአብሮነት ፎረም እየተካሄደ ነው።
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያዊያን የአንድነትና የመከባበር ኃይል የሚያሳይ ትልቅ መሰባሰቢያ መድረክ ነው ሲሉ የበዓሉ ታዳሚዎች ገለጹ።