የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) (ኢ/ር) ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመልዕክታቸውም÷የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ያለውን ፅኑ ፍቅር በመስቀል ላይ ያሳየበት እንዲሁም ይቅርታና ምህረትን ለሰው ልጆች የሰጠበት፤ የጥልና የመለያየት ግድግዳን አፍርሶ የሰውን ልጅ የታደገበት መሆኑን አውስተዋል፡፡
በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩት መንፈሳዊ በዓላት አንዱ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡
ይህ የትንሳዔ በዓል መታዘዝን፣ይቅርታንና ምህረትን እንዲሁም አንዱ ለሌላው መተሳሰብ እንዳለበት የሚያስተምር መሆኑን አንስተዋል፡፡
በዓሉን ስናከብር መረዳዳትንና መጠያየቅን ከተለመደው ባህል ባለፈ በፍጹም መንፈሳዊነት ስሜት በጎዳና ላይ የወደቁትን በማሰብ፣ በህግ ጥላ ስር ያሉትን በመጠየቅ፣ታመው የተኙትን በማጽናናትና ካለን ላይ በማካፈልና በአብሮነት መሆን እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች በደል ተላልፎ በመሰጠት የሰውን ልጆች ከጨለማ ወደ ብርሃን ነጻ ለማውጣት ዋጋ የከፈለበት በመሆኑ እኛም አቅመ ደካሞችን በመርዳትና ካለን በማካፈል፣ለወገኖቻችን በመድረስና በመተሳሰብ በዓሉን ማከበር አለብን ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የትንሳኤ በዓል ለክልሉ ህዝቦች እንዲሁም ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሰላም፣ የበረከት፣ የመተሳሰብና የፍቅር እንዲሆንም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
FBC
More Stories
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ
የጎንጋ ህዝቦች የልማት፥ የወንድማማችነትና የአብሮነት ፎረም እየተካሄደ ነው።
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያዊያን የአንድነትና የመከባበር ኃይል የሚያሳይ ትልቅ መሰባሰቢያ መድረክ ነው ሲሉ የበዓሉ ታዳሚዎች ገለጹ።