የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ በጉበት በሽታ የሚጠቁ ዜጎች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ካለባቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት ብሏል
በዓለም ላይ በየዕለቱ 3 ሺህ 500 ሰዎች በጉበት በሽታ እየሞቱ እንደሆነም ድርጅቱ አስታውቋል
ኢትዮጵያ የጉበት በሽታ እየተስፋፋባቸው ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን የዓለም ጤና ድርጅት ገለጸ፡፡
የዓለም ጉበት በሽታ ጉባኤ በፖርቹጋል ተካሂዷል፡፡
በዚህ ጉባኤ ላይ እንደተገለጸው በዓለማችን በየዕለቱ 3 ሺህ 500 ሰዎች በጉበት በሽታ እየሞቱ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በዓለም ጤና ድርጅት የኤችአይቪ፣ ሄፓ ታይተስ እና ተላላፊ በሽታዎች ፕሮግራም ሃላፊ ሜግ ዶሂርቴ እንዳሉት በጉበት በሽታ ከሚሞቱት ውስጥ 83 በመቶዎቹ በሄፓታይተስ ቢ በተሰኘው የጉበት በሽታ የሚሞቱ ናቸው ብለዋል፡፡
በጉበት በሽታ የሚጠቁ ዜጎች እየጨመረ ነው ያሉት ሃላፊው 63 በመቶ ያህሉ ተጠቂዎች በአፍሪካ የሚገኙ ዜጎች እንደሆኑም ተናግረዋል፡፡
በየዕለቱ ስድስት ሺህ ሰዎች በጉበት በሽታ እየተጠቁ ነው ያለው የዓለም ጤና ድርጅት ተጠቂዎች በቂ ህክምና እያገኙ እንዳልሆነም የዓለም ጤና ድርጅት በድረገጹ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
Al-Ain
More Stories
የለምጽ ምንነት እና ህክምናው
የኮሊስትሮል መድሃኒትን የሰሩት ተመራማሪ ህይወታቸው አልፈ
በኢትዮጵያ ለሕጻናት ክትባት ተደራሽነት ፕሮጀክት 45 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ተደረገ