ማሻ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) የሩሲያ ኑክሌር፣ ራዲዬሽንና ኬሚካል ጥበቃ ኃይል ዋና ኃላፊ ሌተናንት ጀነራል ኢጎር ኪሪሎቭ እና እረዳታቸው በተጠመደ ፈንጂ ምክንያት ሞስኮ ውስጥ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡
ኃላፊው እና እረዳታቸው ሕይወታቸው ያለፈው ሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አቅራቢያ በስኩተር ላይ በተጠመደ ፈንጂ መሆኑን የሀገሪቱ መርማሪ ኮሚቴ አስታውቋል።
300 ግራም የሚመዝነው ፈንጂ በርቀት መቆጣጠሪያ አማካኝነት መፈንዳቱን ዩሮኒውስ ዘግቧል፡፡
ሌተናንት ጄነራሉ የተከለከለ ኬሚካል በዩክሬን ጦርነት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቅደዋል በሚል ዩክሬን ትናንት መክሰሷ ይታወሳል፡
More Stories
272 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ
ህብረተሰቡን በማህበራዊና ኢኮኖም ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉም ልደግፍ እንደምገባ የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር ገለፀ።
የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር 11ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ መካሄድ ጀምሯል