October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በእምነቱ አስተምህሮ ከተጫነበት ተራራ ስር ተሰውሮ ከነበረበት ስፍራ ይወጣ ዘንድ በደመራ ሰማያዊ ምልክት የታየበት ቀን የሚከበርበት በዓል ነው ብለዋል፡፡የመስቀል በዓል የአዳዲስ እሳቤዎች የሚነገሩበት ከጨለማ ወደ ብርሃን የምንሸጋገርበት አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት የጠብ ግድግዳ የሚፈርስበት ሰላም የሚሰበክበት ብሩህ ተስፋ የሚሰነቅበት ጊዜ ነው ሲሉም ተናግረዋል ስል የዘገበው የክልሉ መ/ኮ/ጉ/ቢሮ ነው።