የሽኝት መርሐ-ግብሩ ሲጠናቀቅም የቀብር ስርዓቱ በብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ዛሬ 8 ሰዓት ላይ ይፈጸማል።ፕሮፈሰሩ በገጠማቸው የልብ ህመም በሀገር ውስጥ እና በኬኒያ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ማክሰኞ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል፡፡በኢንስቲትዩቱ ለተመራማሪዎች የአጭርና የረጅም ጊዜ ስልጠና በማመቻቸት ሙያቸውን እንዲያሳድጉ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረከቱ ሲሆን፥ ጀማሪ ተመራማሪዎችም አቅማቸውን አጎልብተው ትርጉም ያለው የምርምር ስራ እንዲሰሩ ጥረት ማድረጋቸው ይነገራል፡፡ሁሉም የምርምር ስራዎች ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ከማስቻል ባለፈ የምርምር ውጤቶች ለህብረተሰቡ እንዲደርሱና የሚመለከተው አካልም እንዲጠቀምባቸው በማድረግ ረገድ ጉልህ ድርሻ እንደነበራቸው ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።
የፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የአስክሬን ሽኝት በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ