ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት ዓለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክ መንግሥት መለኪያ ደረጃዋን አሻሻለች፡፡በየሁለት ዓመቱ የሚወጣው የተባበሩት መንግሥታት ዓለም አቀፋዊ የኢ-መንግሥት መለኪያ ትናንት በኒዮርክ ከመንግሥታቱ ስብሰባ ጎን ለጎን ይፋ ሆኗል።ይህ ዓለም አቀፋዊ የኤሌክትሮኒክ መንግሥት መለኪያ የዓለም ሀገራት በየሁለት ዓመቱ ከሌሎች ሀገራት አንጻር እና በራሳቸው ካሳዩት እድገት ጋር በማነጻጸር ሀገራቱ በዘርፉ ያደረጉትን መሻሻሎች ብሎም ያስመዘገቧቸውን ለውጦች የሚያሳይ ነው።በዓለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክ መንግሥት ሪፖርት መሠረት ኢትዮጵያ ከነበረችበት 10 ደረጃዎችን ማሻሻል ችላለች፡፡
FBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ