የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኬኒያ ናይሮቢ የሚገኘው የጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሠራተኞች በስራ ማቆም አድማ ላይ በመሆናቸው ምክንያት ወደ ናይሮቢ የሚያደርገው በረራ በታቀደለት መርኃ ግብር እየተከናወነ አለመሆኑን አስታውቋል። አየር መንገዱ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ እንደሚገኝ በመግለፅ በክስተቱ ለተፈጠረው መስተጓጎል ደንበኞቹን ይቅርታ ጠይቋል። ደንበኞች የበለጠ መረጃ ለማግኘት የዓለም አቀፍ የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል ስልክ ቁጥር በ+251 11 617 9900 ወይም በ 6787 በመደወል አልያም ናይሮቢ የሚገኘውን ትኬት ሽያጭ ቢሮ በአካል በመገኘት ማግኘት እንደሚቻል አየር መንገዱ አስታውቋል።
EBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።