October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ሶስት እስራኤላውያን በዮርዳኖስ ድንበር ተገደሉ

ዮርዳኖስ ከዌስትባንክ ጋር በሚያዋስናት የድንበር መተላለፊያ የተፈጸመውን ጥቃት እየመረመርኩ ነው ብላለች
ሶስት እስራኤላውያን በዮርዳኖስ እና ዌስትባንክ መተላለፊያ ድንበር ተተኩሶባቸው ተገደሉ።
እያሽከረከረ ከወደ ዮርዳኖስ ወደ ዌስትባንክ የገባው ግለሰብም በጸጥታ ሃይሎች መገደሉን የእስራኤል ባለስልጣናት ተናግረዋል።
ህይወታቸው ያለፈው እስራኤላውያን እድሜያቸው ከ50 አመት በላይ የሆነ ወንዶች መሆናቸውን የእስራኤል አስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት ተቋም ገልጿል።
ዮርዳኖስ “አለንቢ” በተሰኘው መተላለፊያ የተፈጸመውን ግድያ እየመረመርኩ ነው ማለቷን የሀገሪቱ ብሄራዊ የዜና ወኪል ፔትራ ኒውስ አስነብቧል።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ግድያውን አጥብቀው ያወገዙት ሲሆን፥ ከኢራን እና ከምታስታጥቃቸው ሃይሎች ጋር የሚገናኝ ጥቃት ነው ብለዋል።

Al-Ain