ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቤይጂንግ ቆይታቸው ከቻይና ኮሙኒኬሽን እና ኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሲሲሲሲ) ጋር ከጥቂት ወራት በፊት የተጀመረውን ውይይት ዛሬ ቀጥለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሲሲሲሲ የኢትዮጵያን ከተሞች በማዘመን የተጫወተውን ሚና ማድነቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት መረጃ ያመለክታል፡፡ ከቻይና ጭምር የሌላ ሀገራት ቱሪስቶችን በሰፊው የመሳብ ትልም እውን ለማድረግ ሆቴሎችን፣ አውሮፕላን ማረፊያዎችን እና ተያያዥ አገልግሎቶችን መገንባት ቁልፍ እንደሆነም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል።
EBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።