October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሀገር ዕድገትና ብልፅግና ወሳኝ ድርሻ አለው – አቶ አሕመድ ሺዴ

 የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሀገር ዕድገት እና ብልፅግና ወሳኝ ድርሻ አለው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ ገለጹ፡፡

አቶ አሕመድ ሺዴ በቅርቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ከኢፌዴሪ አየር ኃይል የተለያዩ ክፍሎች ከተውጣጡ የሰራዊቱ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

በመድረኩ በሰጡት ማብራሪያ÷ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቁም ባለፈ የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።

ይህም የኢትዮጵያን ዕድገት እና ብልፅግናን ወደ ተሻለ ከፍታ እንደሚያሸጋግር ተናግረዋል።

የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው÷ በተቋሙ ያሉ የሰራዊቱ አመራሮች የመንግስትን የኢኮኖሚ ፖሊሲ በበቂ ሁኔታ መረዳታቸው ቀጣይ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲመሩ እንደሚያስችል መጥቀሳቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

FBC