በስልጤ ዞን ሰሞኑን በተከሰተው የጎርፍ አደጋ የተፈናቃይ ቁጥር እየጨመረ በመሆኑ እየተደረገ ያለው ሰብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዞኑ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ጽ/ቤት ጥሪ አቅርቧል፡፡ የፅ/ቤቱ ኃላፊ ወሲላ አሰፋ ለኢቢሲ ሳይበር እንደገለፁት፤ በጎርፉ አደጋው 7ሺ ሰዎች ተፈናቅለዋል፤ 1300 ሄክታር መሬት ማሳ ከጥቅም ውጭ ሆኗል፤ 6 ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 1ሺ ቤቶች በጎርፍ ተውጠዋል፡፡ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በስልጢ እና ምስራቅ ስልጢ ወረዳዎች በደረሰው የጎርፍ አደጋ እየተፈናቀሉ ያሉ ሰዎች ቁጥር አሁንም እየጨመረ መሆኑን ኃላፊዋ ገልፀዋል፡፡ በሁለቱ ወረዳዎች በጎርፍ ተውጠው የነበሩ ቀበሌዎች ከ6 ወደ 8 ማደጋቸውንና በውሃ የተዋጡ ትምህርት ቤቶች ቁጥር 6 መድረሱን ተናግረዋል፡፡
Woreda to World
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።