October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የኢለን መስኩ ኒውራ ሊንክ ሁለተኛውን ቺፕ በሰው ልጅ አዕምሮ ውስጥ ገጠመ

ኒውራሊንክ ኩባንያ በነርቭ ጉዳት ምክንያት የመንቀሳቀስ ችግር ላጋጠማቸው ሰዎች ተስፋን ይዞ ቺፑ የተገጠመለት ሰውም ነርቮቹ መንቀሳቀስ ጀምረዋል ተብሏል

መጥቷልየኢለን መስኩ ኒውራ ሊንክ ሁለተኛውን ቺፕ በሰው ልጅ አዕምሮ ውስጥ ገጠመ፡፡የአሜሪካዊው ቢሊየነር ኢለን መስክ ንብረት የሆነው የባዮ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ኒውራሊንክ ባለፈው ጥር ወር የመጀመሪያውን ችፕስ በሰው አእምሮ ውስጥ መቅበሩ ይታወሳል፡፡የመስክ ባዮቴክ ኩባንያ የ30 አመት እድሜ ባለው ግለሰብ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ችፕስ የገጠመው ባለፈው ጥር ወር ነበር።ኩባንያው አሁን ደግሞ ሁለተኛውን ሙኩራ አሌክስ በሚል ስም ለሚጠራ አካል ጉዳተኛ አዕምሮ ውስጥ መግጠሙን እና ግለሰቡም ለውጥ ማሳየት ጀምሯል ብሏል።የሳንቲም መጠን ያላትን ቺፕስ የሰው ልጅን እንቅስቃሴ ፍላጎት ከሚያዘው የአእምሮ ክፍል ላይ በቀዶ ጥገና እንድትቀመጥ የሚደረግ ነው።ይህቺ ቺፕስ የአእምሮን እንቅስቃሴ በመመዝገብ እና የእንቅስቃሴ ፍላጎትን ወደሚተረጉም ማቀላጠፊያ መተግበሪያ ወይም አፕ ለማስተላለፍ ጥቅም ላይ ትውላለች።

AL-AIN