የታጋቾች ቤተሰቦች የኔታንያሁ አስተዳደር ተኩስ በማቆም ወገኖቻቸውን እንዲያስለቅቅ መጠየቃቸውን ቀጥለዋል
አል ዐይን ኒውስቀዳሚ ገፅዜናአስተያየትፖለቲካኢኮኖሚማህበራዊልዩልዩስፖርትየመረጃ ሳጥንተመልከትፖለቲካየእስራኤል ጦር የስድስት ታጋቾችን አስከሬን ከካን ዩኒስ ማስወጣቱን ገለጸየታጋቾች ቤተሰቦች የኔታንያሁ አስተዳደር ተኩስ በማቆም ወገኖቻቸውን እንዲያስለቅቅ መጠየቃቸውን ቀጥለዋልአል-ዐይን 2024/8/20 11:48 GMTየአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እስራኤል የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማቷን ተናግረዋልየእስራኤል ጦር በደቡባዊ ጋዛ ካን ዩኒስ ስድስት ታጋቾች ተገድለው መገኘታቸውን አስታወቀ።ጦሩ ሟቾቹ ያጌዝ ቡችሽታብ፣ አሌክሳንደር ዳንሲይግ፣ አቭራሃም ሙንዱር፣ ዮራም ሜትዝገር፣ ናዴቭ ፖፕልዌል እና ቻይም ፔር መሆኗቸውን ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል።አስከሬናቸው ከካን ዩኒስ እንዲወጣ የገለጸው ጦሩ ለሟቾቹ ቤተሰቦች መርዶ መላኩን አብራርቷል። በጥቅምት 7ቱ የሃማስ ጥቃት ታግተው የተወሰዱ እስራኤላውያን ሞት መቀጠል በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ነቀፌታ እያስከተለባቸው ነው።“ኔታንያሁ በታጋቾች እየቆመረ ነው” ያሉ የታጋቾች ቤተሰቦች በአደባባይ ተቃውሟቸውን ቢያሰሙም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከ100 በላይ ታጋቾችን የሚያስለቅቅ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ከመድረስ ይልቅ “ሃማስን መደምሰስ” ላይ አተኩረዋል በሚል ይወቀሳሉ።
Al-Ain
More Stories
የየመኑ ሃውቲ በማዕከላዊ እስራኤል “ወሳኝ ኢላማዎችን” በድሮኖች መትቻለሁ አለ
እስራኤል የተመድ ዋና ጸኃፊ ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ እግድ ጣለች
እስራኤል በሊባኖስ በፈጸመችው የአየር ላይ ጥቃት ተጨማሪ የሂዝቦላህ ከፍተኛ አመራር መግደሏን አስታውቃለች፡፡