የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገርን ሉዓላዊነት እና ሰላም ከማረጋገጥ ባለፈ በልማቱ ላይ እያደረገ ያለው ተሳትፎ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ገለጹ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር ) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ እንደገለጹት ÷መከላከያ ሠራዊት የሰላም ምንጭ ብቻ ሳይሆን የልማት እና የፈጠራ ምንጭ መሆን ስላለበት በዚህ አግባብ እየተመራ እየተገኘ ያለው ውጤት ተስፋ ሰጭ ነው ፡፡ይህም ተስፋ ሰጭ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ነው ያሉት ።በስንዴ ምርት በእርሻ በ #አረንጓዴዓሻራ ብዙ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በማምረት ልማቱን ለማሳለጥ እና የብልፅግና መሰረት ለመጣል እያደረገ ያለው ጥረት ሊበረታታ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
FBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።