የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾሟል። የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው ለርዕሰ መስተዳድሯ ሹመቱን የሰጠው፡፡ አዲስ ሹመት የተከናወነው ወቅቱ የሚጠይቀውን አሻጋሪ የለውጥ አመራር በማምጣት የህዝቡ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ፍላጎቶች በተገቢው መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ ለማስቻል እንዲሁም የቀድሞው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በገዥው ፓርቲ ለሌላ ተልዕኮ በመፈለጋቸው መሆኑም ተጠቅሷል። ወይዘሮ ዓለሚቱ አሞድ ቀደም ሲል የክልሉ ምክትል አፈ- ጉባኤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆንና በሌሎች የተለያዩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተጠቁሟል፡፡ ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ በክልሉ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ርዕሰ መስተዳድር መሆናቸውም ተገልጿል። በሚፍታህ አብዱልቃድር
EBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።