በአንካራ በተካሄደው ድርድር ኢትዮጵያ የባሕር በር እንደሚያስፈልጋት የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተረዳበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ መንግስት ሰላማዊ እና ህጋዊ በሆነ መንገድ የባሕር በር በጋራ የማልማት እና የመጠቀም እንቅስቃሴውን እንደሚገፋበት ተነግሯል፡፡ ይህ የተገለፀው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ነው፡፡ በሳምንታዊ መግለጫውም በቱርክ አንካራ በሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የተደረገው ሁለተኛው ዙር የሁለትዮሽ ድርድር ተስፋ ሰጭ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
EBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።