የገቢዎች ሚኒስቴር ከመካከለኛ ግብር ከፋዮች ጋር በታክስ ህግ ተገዥነት እና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ፤ የመንግስት ዋነኛ ትኩረት ከግብር የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል። የገቢ አሰባሰቡ ህግና ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን ለማስቻል በመንግስት የሚመራ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው ብለዋል። የሀገር ውስጥ ገቢን ለማሳደግ ተቋማት በጋራ እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል። የገቢዎች ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በበኩላቸው፤ የገቢ አሰባሰቡን ለማሳደግ በቀጣይ ዓመታት 5 ዋና ዋና ስትራቴጂክ እቅዶች ተነድፈው እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል።
Woreda to World
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።