የገቢዎች ሚኒስቴር ከመካከለኛ ግብር ከፋዮች ጋር በታክስ ህግ ተገዥነት እና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ፤ የመንግስት ዋነኛ ትኩረት ከግብር የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል። የገቢ አሰባሰቡ ህግና ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን ለማስቻል በመንግስት የሚመራ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው ብለዋል። የሀገር ውስጥ ገቢን ለማሳደግ ተቋማት በጋራ እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል። የገቢዎች ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በበኩላቸው፤ የገቢ አሰባሰቡን ለማሳደግ በቀጣይ ዓመታት 5 ዋና ዋና ስትራቴጂክ እቅዶች ተነድፈው እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት የመንግስት ዋነኛ ትኩረት ገቢን ማሳደግ ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ተናገሩ።

More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ