በፓሪስ ኦሊምፒክ በማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክለው አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለውድድሩ ሲያደርግ የነበረውን ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡አትሌት ቀነኒሳ በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳስታወቀው÷ ለፓሪሱ ኦሊምፒክ ሲያደርግ የነበረውን ዝግጅት አጠናቋል።በዝግጀቱ አብረውት ለነበሩት የቡድን አሰልጣኞች፣ ለቡድኑ አባላት፣ ለቤተሰቦቹ እና በመላው ዓለም ለሚገኙ አድናቂዎቹ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡እንደ ቡድን ጠንካራ ዝግጀት ማድረጋቸውን የገለፀው አትሌት ቀነኒሳ፤ ጠንካራ የቡድን ስሜት ለመፍጠር የሚያስችል የልምምድ ጊዜ ማሳለፍ መቻላቸውን ገልጿል።
FBC
More Stories
ኢትዮጵያ በፊፋ ደረጃ 147ኛ ሆናለች
ኬቨን ዲብሮይን በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ማንቼስተር ሲቲን እንደሚለቅ ተረጋገጠ
በማሻ ወረዳ በህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት ለተከታታይ 5ቀን ስካሄድ የነበረው የእግርኳስ ውድድር ፍጻሜውን አግኝተዋል።