October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለፓሪስ ኦሊምፒክ ሲያደርግ የነበረውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለፀ

በፓሪስ ኦሊምፒክ በማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክለው አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለውድድሩ ሲያደርግ የነበረውን ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡አትሌት ቀነኒሳ በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳስታወቀው÷ ለፓሪሱ ኦሊምፒክ ሲያደርግ የነበረውን ዝግጅት አጠናቋል።በዝግጀቱ አብረውት ለነበሩት የቡድን አሰልጣኞች፣ ለቡድኑ አባላት፣ ለቤተሰቦቹ እና በመላው ዓለም ለሚገኙ አድናቂዎቹ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡እንደ ቡድን ጠንካራ ዝግጀት ማድረጋቸውን የገለፀው አትሌት ቀነኒሳ፤ ጠንካራ የቡድን ስሜት ለመፍጠር የሚያስችል የልምምድ ጊዜ ማሳለፍ መቻላቸውን ገልጿል።

FBC