ከቀጣይ ሣምንት ጀምሮ ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በመላ ሀገሪቱ እንደሚሠራጭ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡በአዳማ ጉምሩክ ጣቢያ የተለያዩ መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው የቆሙ ከ700 በላይ ተሽከርካሪዎች ዛሬ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ሕግ መጨረሳቸውንም ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ምርቱ ለገበያው በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ በመወያየት የመፍትሔ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል፡፡በዚህም መሠረት የገበያ ሁኔታን በዘላቂነት ለማረጋጋጥ በመንግሥት ወጭ የተገዛው ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በሚቀጥለው ሣምንት በመላ ሀገሪቱ ይሠራጫል ብለዋል፡፡ 468
FBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።