በጀርመን አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ በስፔን አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡ በበርሊን ኦሊምፒክ ስታዲየም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ስፔን እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለአራተኛ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት ሆናለች፡፡ በጨዋታው የስፔንን የማሸነፊያ ግቦች ኒኮ ዊሊያም እና ማይክል ኦያርዛባል በ47ኛው እና በ86ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ እንግሊዝን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ተቀይሮ የገባው ኮል ፓልመር በ73ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡ በውድድሩ አስደናቂ ብቃት ሲያሳይ የቆየው የ17 ዓመቱ ኮከብ ላሚን ያማል በዚህም ጨዋታ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ በማቀበል ውድድሩን በስኬት አጠናቋል፡፡
EBC
More Stories
ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ ነጥብ ተጋሩ
በፕሪሚየር ሊጉ አዳማ ከተማ ባህር ዳር ከተማን 1 ለ 0 አሸነፈ
በ5 ሺህ ወንዶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ሶስት ተከታትለው ገቡ