የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 3ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን በምክር ቤቱ የስብሰባ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ለጉባኤው የተያዙ አጀንዳዎችን ያቀረቡ ሲሆን፤ ምክር ቤቱም የቀረቡትን አጀንዳዎች መርምሮ በሙሉ ድምጽ በማፅደቅ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ምክር ቤቱ በመደበኛ ጉባኤው ላይ የ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትን ጨምሮ ለጉባኤው የተያዙ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
EBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ