የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአዲስ አበባ የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) የተመራ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ አባላት ገለፃ በማድረግ አስጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ከፒያሳ አራት ኪሎ እና ከሜክሲኮ ሣር ቤት የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ ተደርጎባቸዋል። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ፕሮጀክቱ የአፍሪካ መዲና የሆነችውን አዲስ አበባ እንደስሟ አዲስና ልዩ ከተማ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።
EBC
More Stories
ኢትዮጵያ የፊታችን ነሀሴ በአንካራ በሚካሄደው ድርድር ምን ትጠብቃለች?
የአይቻልም እና የአይሆንም መንፈስን መስበር ከተቻለ የማይቻል ነገር የለም “- ተማሪ ወጋየሁ ወራጆ
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ይሰጣሉ