የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ሞተራይዝድ ሻለቃ አሁን ላይ ያለበትን ዝግጁነት ጎብኝተዋል። ፊልድ ማርሻሉ በጉብኝታቸው ሞተራይዝድ ሻለቃው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስታንዳርድ መሰረት ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውን ተናግረዋል። ሞተራይዝድ ሻለቃው በተሟላ የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የተናገሩት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፤ ሻለቃው ለማንኛውም ተልዕኮ ዝግጁ መሆኑን ለማረጋገጥ መቻላቸውንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ በተለይም ለምስራቅ አፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አበርክቶ እንደነበራትም ፊልድ ማርሻሉ አስታውሰዋል።
ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም መረጋገጥ በሙሉ ዝግጁነት ላይ እንደምትገኝ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ገለፁ

More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ