በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ለእግር ጉዞ ወጥቶ ከሳምንት በላይ በተራራማ ስፍራዎች ጠፍቶ የቆየው ግለሰብ ብዙ ውሃ እየጠጣ ህይወቱን ማቆየቱ ተሰምቷል።
ሉካስ ማክሊሽ የተባለው ይህ ግለሰብ በተራራማ ስፍራ ለእግር ጉዞ (ሃይኪንግ) በወጣበት በመጥፋት ለ10 ቀናት ብቻውን አሳልፎ ቤተሰቦቹ ሲያፈላልጉት ቆይተዋል።
በወቅቱ በአካባቢው በተከሰተ ሰደድ እሳት ምክንያት በስፍራው የነበሩ አቅጣጫ ጠቋሚዎች መውደማቸው ግለሰቡ እንደ አወጣጡ እንዳይመለስ አድርጎታል።
እንደወጣ የቀረውን ቤተሰባቸውን አፋልጉን ያሉት ቤተሰቦቹም ለፖሊስ ጥቆማ ሰጥተው፥ በአነስተኛ ሰው አልባ አውሮፕላን በተደረገ ፍለጋ በህይወት መገኘቱ ተሰምቷል።
በወቅቱ ግለሰቡ በተራራማው ስፍራ የድረሱልኝ ጥሪ ያቀርብ የነበረ ቢሆንም፥ በትክክል አቅጣጫው ባለመታወቁ ምክንያት ለቀናት ብቻውን እንዲቆይ አስገድዶት እንደነበርም ነው የተገለጸው።
በተራራማው ስፍራው ቆይታው ታዲያ በሚረግጠው ጫማ ውሃ በማጠራቀም እስከ 4 ሊትር ውሃ በቀን ይጠጣ እንደነበር ተናግሯል።
በወቅቱ ሲገኝ ሰውነቱ ተጎሳቁሎና ከስቶ ቢታይም ለህይወቱ አስጊ አይደለም ተብሏል።
Ahadu Radio
More Stories
የጋዛው ጦርነት የሚቆም ከሆነ ሄዝቦላ በእስራኤል ላይ ጥቃት መሰንዘሩን እንደሚያቆም አስታወቀ
የሀውቲ ታጣቂዎች በእስራኤሏ ሀይፋ ወሳኝ ኢላማ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ገለጹ
በህንድ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓት ላይ በተፈጠረ መተፋፈግ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 121 ደረሰ