በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ጅቡቲ የገባ ሲሆን ከጅቡቲ አቻቸው ማህሙድ አሊ የሱፍ ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም፤ ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማጠናከር እና ቁልፍ ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ የወደብ አገልግሎቶችን በተመለከተ ያላቸውን ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር መደረጉን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል።
EBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ