የኢትዮጵያ አየር መንገደ በዓለም ላይ ምርጡ የአየር መንገድ ነው ሲሉ የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ አምባሳደር ቲቦር ናዥ ገለፁ፡፡

አምባሳደር ቲቦር ናዥ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልእክት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ በአቪዬሽን ዩኒቨርሲቲው ላስመረቃቸው 800 ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
አምባሳደሩ በመልእክታቸውም፤ የኢትዮጵያ አየር መንገደን ብዙ ጊዜ መጎብኘታቸውን ጠቅሰው፤ በነበራቸው ተሞክሮም የአየር መንገዱ የሙያ ልህቀት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ለእኔ የኢትዮጵያ አየር መንገደ በዓለም ላይ ምርጡ የአየር መንገድ ነው ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡
EBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ