የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የችግሩ አሳሳቢነት ግን እየከፋ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
የመንገድ ደህንነትን ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።
በምክክር መድረኩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ÷በኢትዮጵያ የትራፊክ አደጋ የሰው ህይወትን በመቅጠፍ፣አካል በማጉደል እና ንብረትን በማውደም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ተናግረዋል።
የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የችግሩ አሳሳቢነት ግን እየከፋ መሆኑን ገልፀዋል።
በመሆኑም ይህን ችግር ለመከላከል በቅንጅት በመስራት መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በውይይቱ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የመንገድ ደህንነት ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ሲሆን÷ የትራፊክ አደጋን መከላከል ያልተቻለባቸውን ምክንያቶች በመለየት መሠራት ያለባቸው የመፍትሄ ሀሳቦች እንደሚቀመጡ ተገልጿል።
FBC
More Stories
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ
የጎንጋ ህዝቦች የልማት፥ የወንድማማችነትና የአብሮነት ፎረም እየተካሄደ ነው።
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያዊያን የአንድነትና የመከባበር ኃይል የሚያሳይ ትልቅ መሰባሰቢያ መድረክ ነው ሲሉ የበዓሉ ታዳሚዎች ገለጹ።