ሰኔ 16 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 40ኛው የሻንበል አበበ ቢቂላ ማራቶን ውድድር ወደ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም መራዘሙን አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡
በተመሳሳይ ከሰኔ 11 እስከ 15 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 12ኛው ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሰኔ 25 እስከ 29 ቀን እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
ውድድሮቹ የሚካሄዱት በሐዋሳ ከተማ መሆኑን የፌደሬሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡
ፌደሬሽኑ ለሁሉም ክልሎች፣ ከተማ አሥተዳደሮች፣ ክለቦች፣ ተቋማት እና የግል ተወዳዳሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት÷ ምዝገባው እስከ ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን አስታውቋል፡፡
FBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ