የኢራን የሀገርውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩ 6 እጩዎችን ይፋ አድርጓል፡፡
ሚኒስቴሩ በዚህ ወር በሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩ የስድስት እጩዎችን የመጨረሻ ዝርዝር ነው ይፋ ማድረጉ የተሰማው፡፡
ፕሬዚዳንታዊ ምርጫው በቅርቡ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ በሄሊኮፍተር አደጋ ህይዎታቸው ማለፉን ተከትሎ ለሀገሪቱ አዲስ ፕሬዚዳንት መምረጥ በማስፈለጉ ነው የሚካሄደው፡፡
ለፕሬዚዳንትነት ከሚወዳደሩት እጩዎች መካከል በሀገሪቱ በምክትልፕሬዚዳንትነት እያገለገሉ የሚገኙትን አሚርሆሴይን ቃዚዛዴህ ሃሺሚን ን ጨምሮ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች እያገለገሉ ያሉ ሃላፊዎች እንደሚገኙበት የአርቲ ዘገባ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የጋዛው ጦርነት የሚቆም ከሆነ ሄዝቦላ በእስራኤል ላይ ጥቃት መሰንዘሩን እንደሚያቆም አስታወቀ
የሀውቲ ታጣቂዎች በእስራኤሏ ሀይፋ ወሳኝ ኢላማ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ገለጹ
በህንድ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓት ላይ በተፈጠረ መተፋፈግ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 121 ደረሰ