October 5, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

875 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ 875 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡የዛሬ ተመላሾች ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ ፥ ከእነዚህ ውስጥም ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ 18 ታዳጊዎች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።ከሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ሥራ እስካሁን ከ39 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን መመለሳቸው ተጠቁሟል፡፡

FBC