የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ከጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ዋናው መቀመጫው እና የተመሠረተበት ሀገር ደቡብ ኮሪያ ከሆነው ጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት መደረሱን የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈርው መልዕክት አስታውቋል።
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በመልዕክቱ እንደገለጹትም፤ ከበጎ አድራጎት ድርጅቱ ጋር በፅሕፈት ቤታቸው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ለመደገፍ እና በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም ወደ ስራ የሚያስገባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸውን ነው ቀዳማዊት እመቤቷ የጠቀሱት፡፡
EBC
More Stories
እስራኤል በሊባኖስ የከፈተችው ውግያ የጋዛውን ጦርነት ያህል ይከፋ ይሆን?
ዛሬ የ2017 የኢሬቻ ፎረም አካሂደናል።
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)