October 5, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የኢትዮጵያ ስታርትአፕ አዋርድስ መክፈቻ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የኢትዮጵያ ስታርትአፕ አዋርድስ መክፈቻ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

በመርሐ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚልና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዓለም አቀፉ ስታርትአፕ አዋርድስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኪም ባልና የተለያዩ ስታርትአፕ ተወካዮች ተገኝተዋል።

መርሐ ግብሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ ስታርትአፕ አዋርድስ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን÷ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርም ተባባሪ አዘጋጅ ነው።

የኢትዮጵያ ስታርትአፕ አዋርድስ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ የተለያዩ ስታርትአፖች ተወዳድረው ለአሸናፊዎቹ ሽልማት እንደሚሰጥ የዘገበው ኢዜአ ነው።

በዛሬው መርሐ ግብር ኢትዮጵያን ወክለው በምስራቅ አፍሪካ የግሎባል ስታርትአፕ አዋርድስ የሚሳተፉ ስታርትአፖች ይፋ ይሆናሉ።

FBC