ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) 272 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከመጋቢት 18 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 187 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የገቢ እና 84 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች የያዘው፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል ማዕድናት፣ አልባሳት፣ ቡና፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድሃኒትና የውጭ ሀገራት ገንዘቦች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ ነበር የተባሉ 8 ተጠርጣሪዎች እና 7 ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
ፋና
More Stories
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል
ኢትዮጵያ እና ኢንግሊዝ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ኢኮኖሚ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ
አትሌት ትዕግስት አሰፋ አሸነፈች