ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) 272 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከመጋቢት 18 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 187 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የገቢ እና 84 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች የያዘው፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል ማዕድናት፣ አልባሳት፣ ቡና፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድሃኒትና የውጭ ሀገራት ገንዘቦች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ ነበር የተባሉ 8 ተጠርጣሪዎች እና 7 ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
ፋና
More Stories
ህብረተሰቡን በማህበራዊና ኢኮኖም ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉም ልደግፍ እንደምገባ የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር ገለፀ።
የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር 11ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ መካሄድ ጀምሯል
የዘመናት የማሻ ከተማና አካባቢው ህዝብ ጥያቄ የነበረው የመብራት አቅርቦት ችግር የሚፈታ የሳብስቴሽን ግንባታ አልቆ መብራት የማብራት ሙከራ ስራ በስኬት ተጠናቀቀ