ማሻ፣ መጋቢት 2፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ማንቼስተር ዩናይትድ 100 ሺህ ተመልካቾችን የሚያስተናግድ አዲስ ግዙፍ ስታዲየም ሊገነባ መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡
በሁለት ቢሊየን ፓውንድ ወጪ የሚገነባው አዲሱ ስታዲየም በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃልም ነው የተባለው፡፡
ክለቡ ለ115 ዓመታት ያህል ሲገለገልበት ከቆየው ኦልድትራፎርድ አቅራቢያ የሚገነባው አዲሱ ስታዲየም እስከሚጠናቀቅ ድረስ በዛው በኦልድትራፎርድ ጨዋታዎቹን እንደሚያከናውን ተገልጿል፡፡
ክለቡ ይፋ ባደረገው ዲዛይን መሰረት ስታዲየሙ እያንዳንዳቸው 200 ሜትር ከፍታ ያላቸው ሶስት ምሶሶዎች እንደሚኖሩትም የቢቢሲ ስፖርት ዘገባ አመላክቷል፡፡
ኤፍ ኤም ሲ
የአዲሱ ስታዲየም ፕሮጀክት ይፋ ከመደረጉ በፊት ነባሩን ኦልድትራፎርድ ማደስ አልያም አዲስ ስታዲየም መገንባት በሚለው ጉዳይ ላይ ሰፊ ውይይት ሲደረግ መቆየቱንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
More Stories
ኢትዮጵያ በፊፋ ደረጃ 147ኛ ሆናለች
ኬቨን ዲብሮይን በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ማንቼስተር ሲቲን እንደሚለቅ ተረጋገጠ
በማሻ ወረዳ በህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት ለተከታታይ 5ቀን ስካሄድ የነበረው የእግርኳስ ውድድር ፍጻሜውን አግኝተዋል።