March 14, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የሐጅ ጉዞ ምዝገባ እስከ መጋቢት 20 ድረስ ተራዘመ

ማሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ1446 ዓ.ሂ ወይም የ2017 ዓ.ም የሐጅ ጉዞ እና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በዚሁ ወቅት፥ የዘንድሮው የሐጅ ጉዞ ምዝገባ በሳውዲ ሐጅ ሚኒስቴር መመሪያና ፈቃድ መሠረት የሚካሄድ መሆኑን ጠቅሰው፤ ምዝገባው እስከ ረመዷን 29 (መጋቢት 20) ድረስ መራዘሙን ገልፀዋል።

በዘንድሮው የሐጅ ጉዞ 10 ሺህ ሑጃጆችን ለማሳተፍ መታቀዱን ጠቅሰው፤ ምዝገባው በሀገሪቱ ዙሪያ በሚገኙ 30 የምዝገባ ጣቢያዎች በቴክኖሎጂ ታግዞ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የሐጅ ጉዞ ምዝገባው እስከ መጋቢት 20/2017 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን በማብሰር በዚህ ዓመት ሐጅ ለማድረግ አቅሙና ፍላጎቱ ያላቸው ምዕመናን በአቅራቢያቸው ባሉ የምዝገባ ጣቢያዎች ተገኝተው እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢቢሲ