ማሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ1446 ዓ.ሂ ወይም የ2017 ዓ.ም የሐጅ ጉዞ እና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በዚሁ ወቅት፥ የዘንድሮው የሐጅ ጉዞ ምዝገባ በሳውዲ ሐጅ ሚኒስቴር መመሪያና ፈቃድ መሠረት የሚካሄድ መሆኑን ጠቅሰው፤ ምዝገባው እስከ ረመዷን 29 (መጋቢት 20) ድረስ መራዘሙን ገልፀዋል።
በዘንድሮው የሐጅ ጉዞ 10 ሺህ ሑጃጆችን ለማሳተፍ መታቀዱን ጠቅሰው፤ ምዝገባው በሀገሪቱ ዙሪያ በሚገኙ 30 የምዝገባ ጣቢያዎች በቴክኖሎጂ ታግዞ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የሐጅ ጉዞ ምዝገባው እስከ መጋቢት 20/2017 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን በማብሰር በዚህ ዓመት ሐጅ ለማድረግ አቅሙና ፍላጎቱ ያላቸው ምዕመናን በአቅራቢያቸው ባሉ የምዝገባ ጣቢያዎች ተገኝተው እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢቢሲ
More Stories
272 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ
ህብረተሰቡን በማህበራዊና ኢኮኖም ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉም ልደግፍ እንደምገባ የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር ገለፀ።
የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር 11ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ መካሄድ ጀምሯል