አየር ሃይሉ 167 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ለመምታት በካሄደው ዘመቻ ነው 106 ድሮኖችን መትቶ መጣል የቻለው፡፡
ሰው አልባ አውሮፕላኖቹ በዩክሬን ኦዴሳ፣ ኪየቭ፣ ሱሚ እና ቼርካሲ ግዛቶች ላይ ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ርምጃ እንደተወሰደባቸው መገለጹን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ÷ሩሲያ የወደብ ከተማ በሆነችው ኦዴሳ በፈጸመችው ተዳጋጋሚ ጥቃት ከ160 ሺህ በላይ ዩክሬናዊያን የሃይል አገልግሎት ማግኘት እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡
አየር ሃይሉ በሰው አልባ አውሮፕላኖች ላይ የወሰደው የመከላከል ርምጃም ሩሲያ በዩክሬን ከተሞች ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንደሚቀንስ አመላክተዋል፡፡
ፋና
More Stories
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።
ከኢፌዲሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ