ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በኢትዮጵያ የሚገኙት የእንግሊዟ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር በሀገሪቱ መንግሥት የተራድኦ ድርጅት የተገዙ 12 አምቡላንሶችን ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል።
አምቡላንሶቹን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ ተረክበዋል።
አምቡላንሶቹ ለእናቶችና ህፃናት አስቸኳይ ሰብዓዊ አገልግሎት የሚውሉ የህክምና ግብዓቶችን ያሟሉ መሆናቸውም ተመላክቷል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ሰብዓዊ ተግባራትን የጎበኙ ሲሆን ከማኅበሩ አመራሮች በትብብር በሚሰሯቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
More Stories
በዞኑ ከ48 ሺህ 3መቶ በላይ ለሚሆኑ ህጻናት የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት እንደሚሰጥ የሸካ ዞን ጤና መምሪያ ገለፀ።
የጤና አገልግሎትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው – ዶ/ር መቅደስ ዳባ
የጥርስን ጤና መጠበቅ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። የጥርሳችንን ንፅህና መጠበቅ መልካም የአፍ ጠረን እንዲኖረን ከማድረጉ ባለፈ የድድ እና ከአፍ ጋር በተገናኘ የሚፈጠሩ በሽታዎችን እንደሚከላከል የጥርስ ሀኪሞችን አናግሮ ሲኤንኤን ዘግቧል።