የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ አገራቸው ጦርነቱን በሰላም ለመቋጨት በተካሄደው የሳውዲ አረቢያ የሰላም ንግግር ላይ እንድትገኝ አለመጋበዟ የሚያስገርም ነው ማለታቸውን ተከትሎ ትራምፕ ጠንከር ያለ ወቀሳ አቅርበዋል።
የዩክሬን ምላሽ ያልጠበቁት እንደሆነ የገለፁት ትራምፕ፤ ለጦርነቱ ጅማሮ ዩክሬንን ተጠያቂ አድርገው አገሪቱ “ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር” ብለዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት ይህን ማድረግ ይችሉ ነበር፤ ችግሩ በቀላሉ ሊፈታ ይችል ነበር ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል።
እንደ ቢቢሲ ዘገባ፥ ዩክሬን ጦርነቱን መጀመር አልነበረባትም፤ ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር ብለዋል።
ይህም ከሞላ ጎደል ሁሉንም መሬት ያስገኝላት ነበር፤ ሰዎች አይሞቱም ነበር፣ ከተሞችም አይፈርሱም ነበር ሲሉ ነው ትራምፕ የተናገሩት።
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ