ማሻ፣ ጥር 29፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ብራዚላዊው የቀድሞው የሪያል ማድሪድ ተከላካይ ማርሴሎ ከእግር ኳስ ራሱን ማግለሉን አስታወቀ፡፡
የግራ መስመር ተከላካዩ ማርሴሎ በሪያል ማድሪድ ቤት ስኬታማ ጊዜን ያሳለፈ ሲሆን 5 የሻምፒዮንስ ሊግ እና 6 የላሊጋ ዋንጫዎችን ከሎስ ብላንኮቹ ጋር ማንሳት ችሏል፡፡
ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደግሞ 58 ጊዜ ተሰልፎ በመጫዎት 6 ጎሎችን በስሙ አስመዝግቧል፡፡
ከሪያል ማድሪድ በመውጣት በግሪኩ ኦሎምፒኮስ እና በብራዚሉ ፉለሉሜንሴ ያልተሳካ ጊዜያት ያሳለፈው ማርሴሎ ከደቂቃዎች በፊት በለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል በይፋ ጫማ መስቀሉን አስታውቋል፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሊቨርፑል ከአስቶን ቪላ ጋር ይጫወታሉ
አርሰናል ከካራባኦ ዋንጫ ተሰናበተ
ስኬት በጠንካራ ሥራ ብቻ እንደሚገኝ የሚያስተምረው የክርስቲያኖ ሮናልዶ ሕይወት