አሁን ላይ ከእንሰት ተክል አስተዋፅኦዎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ ምክንያት በዘርፉ ጥናትና ምርምሮች እየተከናወኑ መሆናቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ።
በዚህም እንሰት ለምግብነትና ለተለያዩ የቤት ቁሳቁስ ሆኖ ከመዋል አልፎ ተረፈ ምርቱ በፋብሪካ ውስጥ ገቢቶ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ በመሆኑ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ተስጥቶ እየተሰራ ይገኛል።
የአንድራቻ ወረዳ እርሻ፣ደን፣አከባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ፅ/ቤት በበጀት ዓመቱ 12 ሚሚልዮን የእንሰት ችግኝ ለመትከል ቅድመ ዝግጂት እያደረገ እንደሚገኝ የገለጹት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ሸነኖ ከባለፈው አመት ጀምሮ የችግኝ ዝግጅት እንዲደረግ ከአርሶ አደሮች ጋር በመግባባት ሰፋፍ ስራዎች ስሰሩ መቆየቱን አመላክተዋል።
በተያዘው አመት የተጣለውን ግብ ለማሳካት በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ልደግፉና በጋራ መስራት እንደሚገባም ጽ/ቤቱ አሳስበዋል።
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ