የበሽር አላሳድን የ 24 አመት ስልጣን በገረሰሰው የትጥቅ ትግል ውስጥ ወሳኝ ሚና የነበረው ሙርሃፍ አቡ ቋስራ የመከላከያ ሚኒስትር ሆኖ ተሾሟል
የቀድሞ የሶሪያ አማጺዎች ተዋህደው በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ለመሆን መስማማታቸው ተገለጸ።
በይፋ ያልተሾመው የሶሪያ መሪ አህመድ አል ሻራ ከቀድሞ የአማጺ ቡድን ኃላፊዎች ጋር ሁሉንም ቡድኖች ለማፍርስ እና በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ለማሰባሰብ ትናንት መስማማቱን አዲሱ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር መሀመድ አል በሽር ሚኒስቴሩ የቀድሞ አማጺያንን እና ከበሽር አላሳድ ጦር የከዱ ወታደሮችን በመጠቀም እንደሚዋቀር ባለፈው ሳምንት ገልጸው ነበር።
ሻራ በሀገሪቱ ባሉ በርካታ ቡድኖች መካከል ግጭት እንዳይፈጠር የማድረግ ከባድ ኃላፊነት ወድቆበታል
የበሽር አላሳድን የ 24 አመት ስልጣን በገረሰሰው የትጥቅ ትግል ውስጥ ወሳኝ ሚና የነበረው ሙርሃፍ አቡ ቋስራ የመከላከያ ሚኒስትር ሆኖ ተሾሟል።
በሶሪያ ያሉ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የጓሳ አባላት እና የሀይማኖት ተከታዮች በእርስበርስ ጦርነቱ ወቅት የሱኒ እስላማዊ ህግ ሊመጣ ይችላል በሚል ሲሰጉ ቆይተዋል።
ሻራ እሱ የሚመራው እና የቀድሞው የአልቃኢዳ አጋር ሀያት ታህሪር አልሻም(ኤችቲኤስ) በቀድሞው አገዛዝ ላይ በቀል እንደማይፈጽም እና አናሳ ቁጥር ያላቸውን የሀይማኖት ተከታዮች እንደማይጨቁን በሶሪያ ጉብኝት ላደረጉት ምዕራባውያን ዲፕሎማቶች ተናግሯል።
የሶሪያ አማጺያን በጥቂት ቀናት ውስጥ በፈጸሙት መብረቃዊ ጥቃት ደማስቆን በመቆጣጠር የ 13 አመቱ የእርስበርስ ጦርነት እንዲያበቃ እና የበሸር አላሳድ ቤተሰባዊ አገዛዝ እንዲያከትም አድርገዋል። ከስልጣን የተወገዱት አሳድ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ሩሲያ ኮብልለዋል።
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።