የ19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክብረ በዓል አካል የሆነው የዋዜማው የእራት መርሐ-ግብር በጋሞ ምርምር እና ባህል ማዕከል አዳራሽ እየተካሄደ ነው።በመርሐ-ግብሩ ግብሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ለገሰ ጫፎ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት፣ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ከንቲባዎች እንዲሁም የ76ቱ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ተወካዮችን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።በመርሐ-ግብሩ ለበዓሉ በድምቀት መዘጋጀት የላቀ አፈፃፀም ላላቸው ክልሎች እና አመራሮች በፌዴሬሽን ምክር ቤት እና በአዘጋጁ ክልል አማካኝነት የምስጋና እና የእውቅና ሽልማት ይሰጣል።
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።