አቶ አቶም በክልሉ ሕዝቦች የነፃነት ትግል ውስጥ እጅግ ውድ የሆነ ዋጋ ከከፈሉ የነፃነት ዓርበኞች መካከል በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገልጸዋል፡፡አቶ አሻድሊ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት÷ አቶ አቶም ዕድሜ ዘመናቸውን ለክልሉ ሠላምና ልማት ሲታትሩ የኖሩ ባለ ራዕይ መሪ ነበሩ ብለዋል፡፡ሠላምና መረጋጋትን ለመፍጠር ያበረከቱት አስተዋፅዖ በክልሉ ሕዝብ ታሪክ ውስጥ የላቀ ስፍራ የሚሰጠውና ሲወሳ የሚኖር መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመጀመሪያው ርዕሰ መሥተዳድርና የነፃነት ትግል ዓርበኛ የነበሩት አቶም ሙስጦፋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡

More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ